(የካቲት 01 ቀን 2016ዓ.ም ) በጀርመን የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ልዩ መልእክተኛ እና ባለሙሉሥልጣን ክቡር አምባሳደር ፍቃዱ በየነ ከ Dipl.-Ing. Knut Stegemann የEMT HANDELS-WAREN Company Manager እና Prof.Dr.Ing. Peter Hartwig የ Aaqua &Waste International GmbH Managing Director ጋር በኤምባሲው ተዋያይተዋል ።
በውይይቱም የሁለቱ ካምፖኒ ማኔጀሮች ስለካምፖኒያቸዉ ገለጻ ለክቡር አምባሳደሩ ያቀረቡ ሲሆን EMT HANDELS-WAREN በዘመኑ ቴክኖሎጂ በባትሪ የሚሰሩ የዲሊቨሪ ሞተር እና ተሽከርካሪ የሚያመርት ፤ Aaqua &Waste International GmbH ደግሞ በመኖሪያ ቤቶች ላይ የሚገጠሙ የንጹህ መጥቶ ዉሃ ቴክኖሎጂ ፕሮጀክቶችን አስተዋዉቀዋል። በኢትዮጵያ በቅድመ ቢዝነስ ጉዞ እና ኢንቨስትመንት ጉብኝት ለማድረግ ፍላጐት እንዳላቸው ለአምባሳደሩ ገልጸዋል ።
ክቡር አምባሳደር በውይይቱ ወቅት በኢትዮጵያ ስላለው የኢንቨስትመንት ዕድሎችና አማራጮች ገለጻ ያደረጉ ሲሆን ካምፖኒዎቹ ወደ ኢትዮጵያ ለመሄድ ፍላጎት ማሳየታቸዉን በማመስገን ኤምባሲው ድጋፍ እንደሚያደርግላቸው ገልጸውላቸዋል ::

Disclaimer: The official text of the Embassy Website is the English language version. Any discrepancies or differences created in translations are not binding and have no legal effect for compliance or enforcement purposes.

X
Twitter
Facebook