(ሐምሌ 10፣2015 ዓ.ም ) በበርሊን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ልዩ መልዕክተኛ እና ባለሙሉስልጣን ክቡር አምባሳደር ፍቃዱ በየነ እና የሚስዮኑ ባልደረቦች በተገኙበት የአንድ ጀምበር 500 ሚሊዮን የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሀ-ግብር በበርሊን የኢፌዲሪ ኤምባሲ ጽ/ቤት ተካሂዷል።
ክብር አምባሳደር ፍቃዱ በየነ በተዘጋጀዉ የችግኝ ተከላ መርሐ-ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር በመላዉ ሀገራችን በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ አነሳሽነት በየዓመቱ እየተካሄደ ያለው የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ ኢትዮጵያን አረንጓዴ በማልበስ በአየር ንብረት ለውጥ የሚከሰቱ ችግሮችን ለመቀነስ ትልቅ ፈይዳ እንዳለው ገልጸዋል ።
 

Disclaimer: The official text of the Embassy Website is the English language version. Any discrepancies or differences created in translations are not binding and have no legal effect for compliance or enforcement purposes.

X
Twitter
Facebook